ነሐሴ 27፣ 2024 አራታ ቢዮሌሳ ኦሮሚያ (ONM-ABO)
የኦሮሞ ህዝብ ክንድ እና ጋሻ፣ አንበሶቹ የደቡብ ምስራቅ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የመደ ወላቡ ጭብራ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊትን እናስሳለን በሚል ስም ተሰማርቶ ሰላማዊ ህዝብን ሲያሰቃይ በቆየው ጠላት ላይ አኩሪ እና የማያዳግም እርምጃ ወስዷል።
በዚሁ ሁኔታ ነሐሴ 9፣ 2024 በምስራቅ አርሲ ዞን በሮቤ ወረዳ ጄላ ገዳምሳ ቀበሌ ኦዳኮ በተባለ ልዩ ቦታ ውስጥ ሰላማዊ ህዝብ በሚኖርባቸው አካባቢ በመሄድ “እናንተ ናችሁ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊትን የምትመግቡትና ሲጠማውም የምታጠጡት!” በማለት እያሰቃየ የቆየውን ጠላት አድፍጦ በወሰደው እርምጃ አምስት ወታደሮችን ሲገድል ሰባቱን ደግሞ በማይሽር ቁስል ሸኝቷል።
ከሞቱት የፋሺስት ብልፅግና ወታደሮች ውስጥ አዛዥ ቃሲም በመገደሉ አስከሬኑ በመኪና ወደ ትውልድ ቦታው ወደ ምስራቅ ኦሮሚያ መወሰዱ የኦነሰ የእካባቢው ቃል አቀባይ አሳውቋል።
#የሺኒጋው_ቃልኪዳን_ዘመቻ ይቀጥላል!
የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ያወጀው የሽኒጋ ቃል-ኪዳን ዘመቻ የኦሮሞ ህዝብ ነፃነት እና የሀገር ባለቤትነት እስኪረጋገጥ ድረስ በተለየ መልኩም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሎአል።
ድል ለኦሮሞ ህዝብና ለጭቁን ብሔር ብሔረሰቦች!
