ሚያዚያ 11/2024 የኦሮሞ ነጻነት ቄሮ (QBO)
የጃል በቴ ኡርጌሳን ግድያ ምክንያት በማድረግ የገበያ አድማ እና የትራንስፖርት እቀባ፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 13/2024 ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ይጀመሬል። ከእሁድ ጠዋት ጀምሮም የመጨረሻው ቀን ይፋ እስከሚደረግም ተጠናክሮ ይቀጥላል። ይህንንም ሳምንት “የሐዘን ሳምንት” ብለን ሰይመነዋል።
የትራንስፖርት እገዳ እና የገበያ አድማዉም በሕዝብ ተቃውሞም ይታጀባል። በዚሁም የኦሮሞ ነጻነት ቄሮ በውጭ አለም የሚኖረውን የኦሮሞ ህዝብ በሀገሪቱ ያለውን የፋሺስት ብልፅግና አገዛዝን በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቀርቧል።
የኦሮሞ ነጻነት ቄሮ (QBO)
